በላይ ላይ መጨመር (ታህሳስ 1994)

ሰላቶ ቢቸናን በእጁ ውስጥ ሊያስግባ በደንብ ተዘጋጅቶ

ሲያደባ ቆይቶ ሁለገብ ወረራ ሳይታሰብ ክፍቶ

ጀግኖች ተጠራርተው ወጥተው ከቀያቸው

አባኮስትር በላይ በአስቸኳይ ለሁሉም ስምሪት ሰጥቷቸው

በፍፁም ጀግነት አትንኩኝ ባይ ወኔ እየተፋለሙ

ጥቃቱን መክተው ወራሪውን መንጋ አንድ በአንድ ሲለቅሙ

ምድር በደም ቀልማ የጠላት አስክሬን ሲረፈርፍባት

ወገን ድል ለማድረግ በተቃረበበት በዚያች ቀውጢ ስአት

ከመካከላቸው ጀግኖች አንዱን መርጠው

የሞተውን ጠላት ለይተህ ቁጠረው

ብለው አዝዘውት ገና እንደጀመረ ብዙም ሳይገፋበት

በጣም ተቸገረ በላይ በላዩ ላይ እየጨመረበት

Comments

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *